Connect with us

Hi, what are you looking for?

News

የርዕዮት ዜናዎች፡ ጥር -06-2016

በድሮን ጥቃት ተማሪዎች ተገደሉ

በአማራ ክልል መርሐቤቴ ወረዳ ከአንድ ትምህርት ቤት አቅራቢያ በተፈጸመ የድሮን ጥቃት ሁለት ሰዎች ሲገደሉ ቢያንስ አራት ሰዎች እንደቆሰሉ ነዋሪዎች እና የትምህርት ቤቱ አስተዳደር ገለጹ።

በሰሜን ሸዋ ዞን በምትገኘው መርሐቤቴ ወረዳ ዓለም ከተማ የድሮን ጥቃቱ የተፈጸመው ባለፈው ሳምንት ዓርብ ጥር 3/2016 ዓ.ም. መሆኑን ሦስት ነዋሪዎች እና የትምህርት ቤቱ አስረድተዋል።

ከቀኑ ሰባት ሰዓት ገደማ የተፈጸመው ጥቃት ያረፈው አርበኞች አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መግቢያ አካባቢ መሆኑ የትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህር አቶ አሻግሬ አበበ ተናግረዋል።

ሁለት የከተማዋ ነዋሪዎች እንደሚያስረዱት በትምህርት ቤቱ አቅራቢያ ጥቃቱ የተፈጸመው በአካባቢው በሚገኘው “ካርል” የተባለ መናፈሻ ውስጥ የፋኖ ታጣቂዎች ይገኛሉ በሚል ነው።

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የሀገራዊ ምክክር ሂደቶችን ለማከናወን ዝግጅት እየደረገ መሆኑን አሳወቀ

ግጭት በተከሰተባቸው አካባቢዎች የሀገራዊ ምክክር ሂደቶችን ለማከናወን ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ ገልጸዋል።

ኮሚሽነሩ ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ነፍጥ ያነሱ ወገኖች በሰላማዊ መንገድ ወደ ምክክሩ እንዲመጡ መንግስት ለሰላማዊ አማራጭ ቅድሚያ ሰጥቶ ምቹ ሁኔታ በመፍጠር ረገድ የበለጠ መስራት እንዳለበት ተናግረዋል።

ቀደም ብሎ የምክክር ኮሚሽኑን በተመለከተ በሩቅ ሆነው ቅሬታ ሲያነሱ የነበሩ አንዳንድ የፖለቲካ ፓርቲዎች የነበሩ ቢሆንም አሁን ላይ ግን የኮሚሽኑን ትክክለኛ ተልዕኮ በቅርበት በመረዳት በርካታ የፖለቲካ ፓርቲዎች ለሀገራዊ ምክክር ስኬት በጋራ ለመስራት መግባባት መፍጠራቸውን ገልጸዋል።

ኮሚሽኑ እንደ ገለልተኛ ተቋም ከሁሉም ፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በጋራ መስራት እንደሚፈልግ ገልጸው፣ ኮሚሽኑ በሲዳማ፣ ደቡብ ምዕራብ፣ ደቡብ ኢትዮጵያ፣ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ፣ አፋር፣ ቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ ጋምቤላ፣ ሀረሪ፣ አዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ከተሞች የተሳታፊ ልየታ ማካሄዱን አስታውሰዋል። ኮሚሽኑ በትግራይ ክልል ልየታ ያላካሄደ ሲሆን በክልሉ ያለው እቅድ ሳያሳውቅ ቀርቷል።

በትግራይ የሚገኙ ተፈናቃዮች በእርዳታ አቅርቦት እጥረት ለሞትና በሽታ እየተጋለጡ መሆኑ ተናገሩ

በሽረ፣ ዓብይአዲ፣ መቐለ ያሉ የትግራይ ጦርነት ተፈናቃዮች መንግስት ወደቀዬአቸው እንዲመልሳቸው እንዲሁም ዓለምአቀፍ ለጋሾችም የእርዳታ እጃቸው እንዲዘረጉላቸው ጥሪ አቅርበዋል። እንደ ክልሉ አስተዳደር መረጃ በትግራይ አንድ ሚልዮን ገደማ ተፈናቃዮች በትምህርት ቤቶች፣ ግዚያዊ መጠልያ ሸራዎች እንዲሁም ቤተእምነቶች እና ሌሎች ስፍራዎች ተበትነው ይገኛሉ።

ተፈናቃዮች ጦርነቱ ከቆመ ከ15 ወር በኋላ በሚበላ ምግብ እና የሚጠጣ ውሃ እጦት እየተሰቃዩ መሆኑንና ለበሽታ መዳረጋቸውንም ተናግረዋል። ለክልሉ አስተዳደር እና ለፌደራል መንግስቱ ወደቀዬአቸው ለመመለስ በተደጋጋሚ ጥያቄ ቢያቀርቡም ተግባራዊ ምላሽ የለም ይላሉ።

የትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር የጦርነቱ ተፈናቃዮች በፕሪቶሪያው ውል መሰረት ወደቀዬአቸው እንዲመለሱ በተደጋጋሚ እያወጣቸው በነበረ መግለጫ ሲጠይቅ ነበር። የፌደራሉ መንግስት በተፈናቃዮቹ ያለው አቋም እስካሁን አላሳወቀም።

Support Reyot Media:

Go Fund Me: https://gofund.me/afe7b8cb

Patreon: https://www.patreon.com/reyot/about

Follow us:

Twitter: @reyotmedia

Facebook: @ReyotMedia

Instagram: @reyot_media

TikTok: @reyotofficial

Threads: @reyot_media

Click to comment

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Trending

You May Also Like

Sticky Post

ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ትውልድ ይፈርድብናል አሉ በትናትናው እለት በተመረቀው የዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም ተገኝተው ንግግር ያሰሙት ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ የተመረቀው ሙዚየም አገርን ለሆነው ላልሆነውማናወጥ፤...

Sticky Post

የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር አመራሮች እና የህወሓት ከፍተኛ አባላት ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ ጋር ተገናኙ ጠቅላይ ሚኒስተር አብይ አህመድ እና የህወሓት ሊቀመንበር ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል...

Sticky Post

ጠቅላይ ሚኒስተሩ ሹም ሽር አደረጉ በዛሬው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ውሎ የሶስት ሚኒስትሮች ሹመት ጸደቀ። ጠቅላይ ሚኒስተር አብይ አህመድ በቅርቡ ከሥልጣን የተሰናበቱትን ምክትል ጠቅላይ...

Sticky Post

ምክር ቤቱ ይፋዊ ይቅርታ ለመጠየቅ መቐለ ገባ በ ሸኽ ሓጂ ሙሐመድ ኢብራሂም ቱፋ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ከፍተኛ አመራሮች የሚመራ የልዑካን ቡድን...