Connect with us

Hi, what are you looking for?

News

የርዕዮት ዜናዎች፤ 24 – ጥር – 2016

ህወሓት የአመራር ማስተካከያ ለማድረግ መስማማቱን አስታወቀ

ሕዳር 2 ቀን፣ 2016 ዓ.ም ጀምሮ 41 ቀናት እንደፈጀ በተነገረለት የሕወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ፣ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር አመራር፣ የትግራይ ኃይሎች ከፍተኛ ሹሞች፣ የቀድሞ የፓርቲው አመራር እና ሌሎች የተሳተፉበት ልዩ ስብሰባ መጠናቀቁን ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ ትናንት ማምሻውን ባወጣው የጽሑፍ መግለጫ አስታውቋል።

መደረግ የነበረበት ስብሰባ ቢሆንም፥ ትግራይ በድርቅና ረሃብ ባለችበት ሁኔታ ለ41 ቀናት የዘለቀ ስብሰባ በመቀመጡ ይቅርታ የጠየቀው ህወሓት፥ “ከአሁን በኃላ ግን በሙሉ አቅማችን የህዝባችን ችግር በመፍታት ላይ እንጠመዳለን” ሲል ቃል ገብቷል።

በዚሁ ልዩ መድረኩ የተነሱ እና መግባባት የተደረሰባቸው ጉዳዮች ብሎ 6 ነጥቦች ያስቀመጠው ሕወሓት፥ በስብሰባው ዓለምአቀፋዊ፣ ቀጠናዊ፣ ሀገራዊና ውስጣዊ ጉዳዮች ተነስተው ለትግራይ የሚኖረው ትርጉም በጥልቀት ተዳሰዋል ሲል አስታውቋል። ከዚህ በተጨማሪ በመድረኩ ህወሓት “የስትራተጂ አመራር ድክመት” እንዳለበት ተነስቶ መግባባት እንደተደረሰበት የገለፀ ሲሆን ይህም ለፀረ ዴሞክራሲ ባህርያት ማደግ፣ ሙስናና ብልሹ አሰራር መንገስ፣ ለቡድናዊነት እና ሌሎች ችግሮች እንደዳረጉት አምኗል።

ከዚህ በዘለለ የፕሪቶርያ ውል አፈፃፀም በሚመለከት ግምገማ ማካሄዱ፣ በውሉ መሰረት ተፈናቃዮች አለመመለሳቸው፣ የትግራይ ግዛት አለመመለሱ፣ በጦርነቱ ወቅት ለተፈፀሙ ወንጀሎች የተጠያቂነት ጉዳይ ችላ መባሉ፣ ከፌደራል መንግስቱ ጋር ቀጣይ ፖለቲካዊ ድርድሮች አለመካሄዳቸው መነሳቱ ተገልጿል።

በስብሰባው በትግራይ በፓርቲ እና መንግስት መካከል ያለ መዘበራረቅ እንዲቀር፥ አሰራር እንዲበጅ መግባባት ላይ መደረሱ፣ ከግምገማና ነቀፌታ በኃላ በህወሓት ስትራቴጂካዊ አመራር ላይ ማስተካከያ እንዲደረግ ተሰብሳቢው መወሰኑ፣ በቀጣይ ወደ ፓርቲ ጉባኤ ለመግባት ዝግጅት እንዲደረግ ውሳኔ መተላለፉንም መግለጫው አውስቷል።

በአማራ ክልል የተጣለው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በአራት ወራት ተራዘመ

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው ስብሰባ በአማራ ክልል ባሳለፍነው ነሐሴ ለስድስት ወራት የታወጀውን አስቸኳይ አዋጅ ለተጨማሪ አራት ወራት አራዝሟል።

አሜሪካ ጨምሮ የአውሮፓ አገራትና ተቋማት አዋጁ እንዲነሳ እየጠየቁ የነበረ ቢሆንም መንግስት አሁንም በክልሉ ስጋት አንዳለው የሚያረጋግጠውን አዋጅ አራዝሟል፡፡

አዋጁ በሁለት ተቃውሞ በሶሰት ድምፅ ተአቅቦ በአብላጫ ድምፅ እንደተራዘመም ተገልጿል፡፡

መንግስት የአብን ሊቀመንበር የነበሩትን የምክር ቤት አባል በቁጥጥር ስር አዋለ

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አብን ) የመጀመርያው ሊቀመንበር እና የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አበል የሆኑት ደሳለኝ ጫኔ ትናንት ምሽት በፀጥታ አካላት ከቤታቸው ተይዘው መታሠራቸው ተገለፀ።

የፖለቲከኛው ቤተሰብ መሆናቸውን የገለፁ ሰው ለዶቼ ቬለ እንዳሉት የምክር ቤት አባሉ ምሽት 3 ሰዓት ገደማ አዲስ አበባ ውስጥ ከመኖሪያ ቤታቸው አምስት በሚደርሱ የፀጥታ አካላት “በሕግ ትፈለጋለህ” በሚል ተይዘው መወሰዳቸውን አረጋግጠዋል።

አብን ከተመሠረተ ጀምሮ በፈቃዳቸው ኃላፊነታቸውን እስካስረከቡበት ወቅት ድረስ የፓርቲው የመጀመርያው ሊቀ መንበር ሆነው ያገለገሉት ደሳለኝ ጫኔ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከተወከሉ ጥቂት የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ አባላት መካከል አንደኛው ናቸው።

የፓርቲው ከፍተኛ አመራር ባለፉት ጥቂት ወራት ይደረጉ በነበሩ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤዎች ላይ ሲሳተፉ አልታዩም። የምክር ቤት አባሉ ጥር 23 ቀን፣ 2016 ዓ.ም ቤታቸው መበርበሩን እና በፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ ታሥረው እንደሚገኙ የቤተሰባቸው አባል ተናግረዋል፡፡

Support Reyot Media:

Go Fund Me: https://gofund.me/afe7b8cb

Patreon: https://www.patreon.com/reyot/about

Follow us:

Twitter: @reyotmedia

Facebook: @ReyotMedia

Instagram: @reyot_media

TikTok: @reyotofficial

Threads: @reyot_media

Click to comment

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Trending

You May Also Like

Sticky Post

ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ትውልድ ይፈርድብናል አሉ በትናትናው እለት በተመረቀው የዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም ተገኝተው ንግግር ያሰሙት ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ የተመረቀው ሙዚየም አገርን ለሆነው ላልሆነውማናወጥ፤...

Sticky Post

የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር አመራሮች እና የህወሓት ከፍተኛ አባላት ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ ጋር ተገናኙ ጠቅላይ ሚኒስተር አብይ አህመድ እና የህወሓት ሊቀመንበር ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል...

Sticky Post

ጠቅላይ ሚኒስተሩ ሹም ሽር አደረጉ በዛሬው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ውሎ የሶስት ሚኒስትሮች ሹመት ጸደቀ። ጠቅላይ ሚኒስተር አብይ አህመድ በቅርቡ ከሥልጣን የተሰናበቱትን ምክትል ጠቅላይ...

Sticky Post

ምክር ቤቱ ይፋዊ ይቅርታ ለመጠየቅ መቐለ ገባ በ ሸኽ ሓጂ ሙሐመድ ኢብራሂም ቱፋ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ከፍተኛ አመራሮች የሚመራ የልዑካን ቡድን...