Connect with us

Hi, what are you looking for?

News

የርዕዮት ዜናዎች፤ 27-ጥር-2016

16 ሚሊዮን ሕዝብ የምግብ እጥረት አጋጥሞታል ተባለ

መንግሥት በመላው አገሪቱ 16 ሚሊዮን ሕዝብ የምግብ እጥረት አጋጥሞታል ያለ ሲሆን ገሚሱ ከፍተኛ የሆነ የምግብ እጥረት የገጠማቸው እና አስቸኳይ የምግብ እርዳታ የሚሹ እንደሆነ ታውቋል።

በተለይም በሰሜን ኢትዮጵያ ያሉ ከተሞች እና መንደሮች ያለው የምግብ እጥረት ሁኔታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየባሰ እንደመጣ ከሥፍራው የሚወጡ ዘገባዎች ያሳያሉ። ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ይህን የምግብ እጥረት ለመቅረፍ እየወሰደ ያለው እርምጃ በቂ እንዳልሆነ ይነገራል።

ጠቅላይ ኢታማዦር ሹሙ ኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶቿን ትመክታለች አሉ

የኢትዮጵያን ሉዕላዊነት ለማስጠበቅና “የታሪካዊ ጠላቶቿን” ትንኮሳ ለመከላከል የሀገር መከላከያ ሰራዊት ዝግጁ ነው ሲሉ የጦር ሀይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ተናገሩ፡፡

የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ በሁርሶ ኮንቲጀንት ማሰልጠኛ ማዕከል ለ24ኛ ዙር ያሰለጠናቸውን የአንድነት ኮርስ እጩ መኮንኖችን ማስመረቁን ተከትሎ የተናገሩት ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኝት በመንቀሳቀስ ላይ ባለችበት ወቅት የሀገሪቱ ታሪካዊ ጠላቶቿ መሰረተ ቢስ ክሶችን እያቀረቡ ነው ብለዋል።

ለዚህም የሀገር መከላከያ ሰራዊቱ ልክ እንደሁልጊዜው የሀገሩን ዳር ድንበር ለማስከበር ዝግጁ ነው ብለዋል።

የትምህርት ሚኒስቴር የአደንዛዥ እጽ ስርጭትን መቆጣጠር አልቻልኩም አለ

በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የአደንዛዥ እጽና መድሃኒቶች ተጠቃሚነት ችግሮችን ለመከላከል ሥራዎች ሲሰሩ የቆዩ ቢሆኑም ከችግሩ ስፋትና ባህሪ አንጻር የሚፈለገውን ውጤት ማምጣት እንዳልተቻለ ተገለጸ።

ችግሩን ለመፍታትም አደንዛዥ እጾችና መድሃኒቶች ወደ ተቋማቱ እንዳይገቡ ከባለድርሻ አካላት ጋር የቁጥጥር ስራዎችን ከመስራት ጎን ለጎን በጉዳዩ አሳሳቢነት ዙሪያ መንስኤዎችን፣ ልምዶችንና መፍትሄዎችን መሠረት ያደረጉ የባህሪ ለውጥ ሊያመጡ በሚችሉ የተማሪ ሥልጠናዎች ላይ ማተኮር እንደሚገባ በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አብዶ ናስር ገልጸዋል።

ኃላፊው አክለውም ጉዳዩ የሚመለከታቸው የባለድርሻ አካላት በችግሩ አሳሳቢነት ልክ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በቅንጅትና በትኩረት እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

አሜሪካ በአማራ ክልል የተጣለው አዋጅ መራዘም አሳስቦኛል አለች

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኢርቪን ማስኛ በአማራ ክልል የጣለው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ መራዘም እንደሚያሳስባቸው ገልጸዋል።

አምባሳደሩ በኢምባሲው የፌስቡክ ገጽ ባወጡት አጭር መግለጫ በአማራ እና በኦሮሚያ ክልል ጨምሮ በሀገሪቱ ያሉትን ውስብስብ ችግሮች መፍቻው ብቸኛው መንገድ ንግግር
ነው ብለዋል።

Support Reyot Media:

Go Fund Me: https://gofund.me/afe7b8cb

Patreon: https://www.patreon.com/reyot/about

Follow us:

Twitter: @reyotmedia

Facebook: @ReyotMedia

Instagram: @reyot_media

TikTok: @reyotofficial

Threads: @reyot_media

Click to comment

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Trending

You May Also Like

Sticky Post

ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ትውልድ ይፈርድብናል አሉ በትናትናው እለት በተመረቀው የዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም ተገኝተው ንግግር ያሰሙት ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ የተመረቀው ሙዚየም አገርን ለሆነው ላልሆነውማናወጥ፤...

Sticky Post

የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር አመራሮች እና የህወሓት ከፍተኛ አባላት ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ ጋር ተገናኙ ጠቅላይ ሚኒስተር አብይ አህመድ እና የህወሓት ሊቀመንበር ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል...

Sticky Post

ጠቅላይ ሚኒስተሩ ሹም ሽር አደረጉ በዛሬው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ውሎ የሶስት ሚኒስትሮች ሹመት ጸደቀ። ጠቅላይ ሚኒስተር አብይ አህመድ በቅርቡ ከሥልጣን የተሰናበቱትን ምክትል ጠቅላይ...

Sticky Post

ምክር ቤቱ ይፋዊ ይቅርታ ለመጠየቅ መቐለ ገባ በ ሸኽ ሓጂ ሙሐመድ ኢብራሂም ቱፋ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ከፍተኛ አመራሮች የሚመራ የልዑካን ቡድን...